በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ሶኮሩ ወረዳ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ተጀምሯል።
በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነመራ ቡሊ የበጎ ፍቃድ ሥራ ከልማት ውጤቶች በተጨማሪ ማሕበራዊ ትስስርን መረዳዳትንና ወንድማማችነትን ያጠናክራል ብለዋል።
የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር ባለፈው ዓመት ወጣቶችንና ባለሃብቶችን በማሳተፍ ማሕበረሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።
በዚህ ዓመት ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች የተወጣጡ ወጣቶች በ72 የሥራ ዘርፎች ላይ እንደሚሳተፉ አስረድተዋል። ማሕበረሰቡ ባለሃብቶች ምሁራንና ወጣቶች በጉልበት ገንዘብና እውቀት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።