በኦሮሚያ፣ አማራ፣ ሶማሌ እና ደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች ከ418 ሺህ በላይ ህፃናትን ለመከተብ የኩፍኝ መከላከያ ክትባት እየተሰጠ ነው።
የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባለሙያ ታደሰ ያለው እንደተናገሩት ክትባቱ ከግንቦት 28 እስከ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይቆያል።
በዚህ ዘመቻ 418 ሺህ 569 ህፃናትን ለመድረስ ታቅዶ ክትባቱ በትምህርት ቤቶች፣ ጤና ተቋማት፣ ቤት ለቤት እና ህፃናት በሚገኙበት አካባቢ ይሰጣል።
ማሕበረሰቡ በአካባቢው ያሉ ህፃናትን በማስከተብ የበሽታውን መከላከያ ጥረት እንዲያግዝ ጥሪ ተደርጓል።