የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት አባል ሀገራት ድንበር ተሻጋሪ የሳይበር ደህንነት ስጋቶችን ለመከላከል በትብብር መስራት አለባቸው።
ኢጋድ ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የኢጋድ ቀጣናዊ የሳይበር የተግባር ልምምድ ስልጠና በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።
በመርሐ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያን ጨምሮ ዩጋንዳ፣ ኬንያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ እና ጅቡቲ ተወካዮች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ የኢጋድ ተጠሪ አበባው ቢሆነኝ የሳይበር ደህንነት ስጋትን አስቀድሞ ለመከላከል ዘመኑን የዋጀ ዝግጅት ማድረግ እንደሚያስፈልግ አስታውቀዋል።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ በኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነት ስጋትን መከላከልና ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።