አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) - አንጋፋው የባሕል ሙዚቃ አቀንቃኝ አርቲስት ሰማኸኝ በለው ሥርዓተ ቀብር በዛሬው ዕለት ተፈጽሟል።
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በትናንትናው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ሥርዓተ ቀብሩ ቤተሰቦቹ፣ ወዳጅ ዘመዶቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት በአዲስ አበባ ቡልቡላ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።
ድምጻዊው ለሕዝብ ካበረከታቸው የሙዚቃ ሥራዎች መካከል ነይ ዘመድዬ፣ እንዴት ነሽ፣ ደቦት እንስራ፣ ዘና በይ፣ ባላገር እና ሌሎች ይገኙበታል።