የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከሕገ ወጥ ነዳጅ ንግድ ጋር በተያያዘ ከ350 በላይ ማደያዎች ላይ ርምጃ መወሰዱን አስታወቀ።
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ደስታው መኳንንት (ዶ/ር) እንዳሉት በዓመቱ 4 ነጥብ 5 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን ነዳጅ ለማቅረብ ታቅዶ 4 ነጥብ 2 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን በማቅረብ የዕቅዱን 94 በመቶ ማሳካት ተችሏል።
በዚህም የነጭ ናፍታ ሥርጭት ለማደያዎችና ለክልል 69 ነጥብ 5 በመቶ ለቁልፍ ፕሮጀክቶች 9 ነጥብ 5 በመቶ እንዲሁም ለመንገድ ፕሮጀክቶች 13 በመቶ ለኢንዱስትሪ 7 በመቶ እና ለግብርና 1 በመቶ ድርሻ እንዳላቸው ተገልጿል።
በሆርሙዝ ሰርጥ መዘጋት ምክንያት የተፈጠረውን የነዳጅ ቀውስ መንግሥት የተወጣበት መንገድ ተሞክሮ ሊሆን የሚችል ነው ሲሉ አውስተዋል። በተጨማሪም 688 ግለሰቦችን በሕግ ተጠያቂ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።