ለሦስት ሳምንት ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ተመለሰ

በአቢጃታ ሐይቅ ውሃ መሙላትን ተከትሎ ለሦስት ሳምንት ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ተመለሰ። የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች በመወደቃቸው ምክንያት የተቋረጠው ኃይል በተቀናጁ ጥገና ሥራዎች ተመልሶ ነው።

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) – በአቢጃታ ሐይቅ ውሃ መሙላትን ተከትሎ ለሦስት ሳምንት ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ተመለሰ። የኃይል አቅርቦቱ የተቋረጠው በአቢጃታ ሐይቅ ውሃ መሙላትን ተከትሎ ወደ ኮስትክ ሶዳ ፋብሪካ የሚሄደው የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች በመወደቃቸው መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የአዳማ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ጣሃ አሕመድ ተናግረዋል።

“የተቋረጠውን ኃይል ለመመለስ የሐይቁ ውሃ ሙሌት ፈተና እንደነበር” ብለው ገልጸው በአገልግሎቱ ሠራተኞችና በፋብሪካው ትብብር የኃይል መቋረጡ ትናንት ዘላቂ መፍትሔ አግኝቷል ብለዋል። መስመሩ በእንጨት ምሰሶ መውደቅ በተደጋጋሚ ኃይል መቋረጥ ይከሰት እንደነበር አስታውሰው በዘላቂነት ችግሩን ለመፍታት የእንጨት ምሰሶዎቹን በሰባት የብረት ምሰሶ መተካቱን ተናግረዋል።

ፋብሪካው ኃይል እንዲያገኝ 600 ሜትር ርዝመት ያለው የመስመር ዝርጋታ እንደ አዲስ በመስራት ስምንት ተጨማሪ የእንጨት ምሰሶ በድምሩ 15 ምሰሶዎች መተከላቸውን ነው የገለጹት። የጥገና ሥራውን የቡልቡላ አገልግሎት መስጫ ሠራተኞች ከሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቃቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዋር አብራር ለፋና ዲጂታል ገልጸዋል።

ይህ ድረ-ገጽ ኩኪዎችን ይጠቀማል

የእኛን ጣቢያ ለማሻሻል ለትንታኔ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። የእኛን የሚስጥር ፖሊሲ አንብቡ የሚስጥር ፖሊሲ ለተጨማሪ መረጃ።
ውድቅ አድርግ