የዩጋንዳው ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪ ቴንጌ ቴንጌ በአዲስ አበባ ለአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ተሳታፊ ሆኗል።
ቴንጌ ቴንጌ በቲክ ቶክ ላይ ባቀረባቸው የዳንስ እና አክሮባቲክስ ስራዎች ዓለም አቀፍ ዝናን አግኝቷል። በቅርብ ጊዜ ደግሞ ይህንን እውቅናውን ለማህበራዊ አገልግሎት እየተጠቀመ ይገኛል።
ጉባኤው “ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ለተሻለች አፍሪካ” በሚል መሪ ሃሳብ ይካሄዳል። ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የይዘት ፈጣሪዎች በአዲስ አበባ ይሳተፋሉ።
የአፍሪካን ልዩ ታሪክ ለማስተዋወቅ፣ በአገሮች መካከል ትብብርን ለማጠናከር እና የአህጉሪቱን ገጽታ በትክክል ለማስተዋወቅ ይረዳል ተብሏል። ጉባኤው በፐልስ ኦፍ አፍሪካ እና ኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ በመተባበር በዓድዋ ድል መታሰቢያ ይካሄዳል።