በየዓመቱ ሐምሌ 19 የሚከበረው የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል በቁልቢ እና በሀዋሳ በታላቅ ሀይማኖታዊ ስርዓት እየተከበረ ይገኛል።
በቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም በተካሄደው በዓል ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት ስራ አስኪያጅ ብጹዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ብጹዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ እና ሌሎች ጳጳሳት ተገኝተዋል።
በሀዋሳ ከተማ በተካሄደው በዓል ላይ የሲዳማ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ ተገኝተዋል።
ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የመጡ ተከታዮችና ጎብኚዎች ታቦተ ህጉን በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች በድምቀት አክብረዋል።