የትግራይ ሰላምና ለውጥ ምክር ቤት በትግራይ ክልል ሕዝብ ላይ የሚደረገውን አፈና ለመቃወም የፊታችን ቅዳሜ በመስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
የሰላማዊ ሰልፉ አዘጋጅ የትግራይ ሰላምና ለውጥ ምክር ቤት የሚዲያ ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ከበደ አሰፋ መግለጫ ሰጥተዋል።
ሰልፉ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል። አቶ ከበደ ሕገ ወጡ የሕወሓት ቡድን በትግራይ ክልል ሕዝብ ላይ ዘርፈ ብዙ አፈና እና ስቃይ እያደረሰ እንደሆነ ተናግረዋል።
የሰልፉ አላማ ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ እና የፌዴራል መንግሥት እንዲያውቁና ርምጃ እንዲወሰዱ ማድረግ ነው። አዘጋጆቹ መላው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በመሳተፍ ድምጻቸውን እንዲያሰሙ ጥሪ አቅርበዋል።