የትግራይ ዴሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀመንበር አረጋዊ በርሔ ሕገወጡ የሕወሓት ቡድን የትግራይ ሕዝብ የዘመናት መከራ ምንጭ ሆኖ ቀጥሏል ሲሉ ተናገሩ።
አዲስ አበባ ሐምሌ 7 2018 ዓም አረጋዊ በርሔ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተግባራዊ እንዳይሆን ቡድኑ እንቅፋት ሲፈጥር መቆየቱን ገልጸዋል። ቡድኑ ሰላማዊ የፖለቲካ አማራጮችን በመዝጋት ከሻዕቢያ ጋር ጥምረት መፍጠሩንና የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር በኃይል ማፍረሱን አንስተዋል።
እነዚህ ተግባራት ለትግራይ ሕዝብ የተፈጠረውን እፎይታ እያደናቀፉ ለስደትና ለከፋ ድህነት እየዳረጉት መሆኑን ተናግረዋል። የትግራይ ወጣቶችን ወደ ጦር ካምፕ በመውሰድ ለሻዕቢያና ለሱዳን በመሸጥ ገቢ ምንጭ እያደረጋቸው እንደሆነ አክለዋል።
የትግራይ ሕዝብና በውጭ ያሉ ተወላጆች የቡድኑን ጥፋት ለማስቆም በጋራ እንዲሰሩ ጠይቀዋል። ዓለም አቀፍ ተቋማትም የቡድኑን ተግባር በማጋለጥ ሕዝቡን ሊታደጉ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።