ሂዩማን ራይትስ ዎች የሕወሃት ቡድን በትግራይ ክልል ከኤፕሪል ጀምሮ ህገ ወጥ አስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ።
ድርጅቱ በተለያዩ አካባቢዎች የተደረጉ 18 ቃለ መጠይቆች መሰረት ስድስት ጉዳዮችን አረጋግጧል። ቡድኑ ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎችን ጨምሮ ሰዎችን በቤት ለቤት ፍተሻ እና ከወርቅ ቁፋሮ ቦታዎች በማገት እያፈሰ ነው።
ይህ እንቅስቃሴ በክልሉ ነዋሪዎች መካከል ከፍተኛ ፍርሃት ፈጥሯል። ሂዩማን ራይትስ ዎች ቡድኑ ወዲያውኑ እንዲቆም እና የተወሰዱ ታዳጊዎች እንዲለቀቁ ጠይቋል።
በተጨማሪም ከአፈሳው ለማምለጥ የሞከሩ ታዳጊዎች ወላጆች ላይ የማሰር እና የማዋከብ ድርጊቶች ተከስተዋል።