የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ደሳለኝ አምባው (ዶ/ር) ዜጎች በባንኮችና ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ገንዘባቸውን ያለስጋት እንዲያስቀምጡ መተማመኛ እንደሚሰጥ ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ)። የፈንዱ ዓላማ በባንኮችና ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት የመውደቅ ችግር ቢያጋጥም አስቀማጮች በሕጉ መሠረት ካሳ እንዲያገኙ ማድረግና የፋይናንስ ሥርዓት እንዲረጋጋ አስተዋጽኦ ማበርከት ነው።
የመድን ፈንዱ ተጠሪነቱ ለብሔራዊ ባንክ ነው። ከልማት ባንክ ውጭ ሁሉም ባንኮች እና ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት የፈንዱ አባል ናቸው። ከአባል ተቋማት 23 ቢሊየን ብር የሚጠጋ አረቦን መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።
ከተሰበሰበው አረቦን ውስጥ 21 ቢሊየን የሚጠጋው ብር የተሰበሰበው ከመደበኛ ተቀማጭ ገንዘብ ሲሆን ቀሪው ከወለድ ነጻ ተቀማጭ ገንዘብ ነው። ከገንዘብ አስቀማጮች 97 በመቶ የሚሆኑት ከ100 ሺህ ብር በታች ያስቀመጡ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።