በ29ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ነገሌ አርሲ እና ፋሲል ከነማ ያለምንም ግብ አቻ ተለያዩ። ጨዋታው በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ተካሄደ። ኢትዮጵያ ቡና ከወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ምሽት 12 ሰዓት ጨዋታ ያደርጋሉ።
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ29ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ነገሌ አርሲ እና ፋሲል ከነማ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል።
ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች ግብ ሳያስቆጥሩ ወጥተዋል። በዚህ ስታዲየም ኢትዮጵያ ቡና ከወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
አስቀድሞ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም መቐለ 70 እንደርታ እና ሀድያ ሆሳዕና 1 አቻ መለያታቸው ይታወቃል። በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ላይ መደረግ የጀመረው የአርባ ምንጭ ከተማ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንን ጨዋታ ያለ ምንም ግብ ቀጥሏል።