ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 0 በማሸነፍ የ2018 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ሆኗል።
ዛሬ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሊጉን ዋንጫ አንስቷል። ሁለቱ ቡድኖች እስከ መጨረሻው ጨዋታ ድረስ በነጥብ እኩል ነበሩ።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ግቦች በረድኤት አስረሳኸኝ እና እሙሽ ዳንኤል አስመዝግበዋል። ቡድኑ ነጥቡን ወደ 69 ከፍ አድርጓል።
ይህ ለተከታታይ ስድስተኛ ጊዜ እና በአጠቃላይ ለዘጠነኛ ጊዜ የሊጉ ዋንጫ ማንሳት ነው። የኢትዮ ኤሌክትሪክ ተጫዋች ዳግማዊት ሰለሞን በ24 ግቦች ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሆና አጠናቅቃለች።