ሃላባ ከተማ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው የ2018 የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ፍጻሜ ጨዋታ ጋሞ ጨንቻን በመለያ ምት 4 ለ 3 በማሸነፍ አጠቃላይ አሸናፊ ሆኗል።
የፍጻሜው ጨዋታ በመደበኛ ጊዜ ያለ ግብ ተጠናቅቋል። የዋንጫውን አሸናፊ ለመለየት በተደረገው የመለያ ምት ሃላባ ከተማ አሸንፏል።
በሦስተኛ ደረጃ ጨዋታ ደሴ ከተማ የካ ክፍለ ከተማን 1 ለ 0 በማሸነፍ ተጠናቅቋል። ጨዋታው በአዲስ አበባ ስታዲየም ዛሬ ተካሂዷል።
ይህ ድል ሃላባ ከተማን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ አጠቃላይ አሸናፊ አድርጎታል።