ወላይታ ድቻ እና ነገሌ አርሲ በሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 34ኛ ሳምንት ጨዋታ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።
ጨዋታው በአዲስ አበባ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች ግብ ሳያስቆጥሩ ወጥተዋል።
ሊጉን ሲዳማ ቡና በ61 ነጥብ ሲመራው መቻል በ53 ነጥብ ሁለተኛ ሲሆን ነገሌ አርሲ በተመሳሳይ ነጥብ በግብ ክፍያ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
አቤል ያለው በ14 ግቦች የሊጉን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ሲመራው ናትናኤል ዳንኤል በ13 ግቦች ይከተላል።