በአዲስ አበባ በተካሄደው 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌት ጌታቸው ማስረሻና አትሌት መሰለች አለማየሁ አሸንፈዋል፡፡
ውድድሩ በመስቀል አደባባይ ተካሂዶ 638 አትሌቶች ተሳትፈዋል፡፡ በወንዶች ምድብ አትሌት ባለይልኝ ተሻገር ሁለተኛ ሲሆን አትሌት በላይ ጥላሁን ሦስተኛ ደረጃን ይዟል፡፡
በዴንማርክ ኮፐንሀገን ለሚካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶችን ለመምረጥ ውድድሩ ተዘጋጅቷል፡፡ ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ደረጃ የገንዘብ፣ የመዳልያና የዋንጫ ሽልማት ይበረከታል፡፡