አዲሱ ይሁኔ በቻይናዋ ሺያመን በተካሄደው የወንዶች 5 ሺህ ሜትር ውድድር በ12፡57.32 ሰዓት አሸንፏል።
አዲሱ ይሁኔ በ2026 የዳይመንድ ሊግ ሁለተኛ መዳረሻ በሆነችው ሺያመን ከተማ ውድድሩን አጠናቋል። ይህ ሰዓት የዓመቱ ፈጣኑ እና የውድድሩ አዲስ ክብረ ወሰን ሆኗል።
ቢኒያም መሐሪ ሦስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። በሴቶች 1500 ሜትር ብርቄ ሀየሎም ሁለተኛ ሆናለች።
በሴቶች 3000 ሜትር መሰናክል ኬና ቱፋ አምስተኛ ደረጃን አግኝታለች። ሌሎች ኢትዮጵያውያን አትሌቶችም ተሳትፈዋል።