በአዲስ አበባ የሚካሄደው 24ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ በሚደረጉ የፍጻሜ ውድድሮች ፍጻሜውን ያገኛል። የኢትዮጵያ አትሌቶች በስምንት የፍጻሜ ውድድሮች ይሳተፋሉ።
በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች በተለያዩ የፍጻሜ ውድድሮች ይሳተፋሉ። አመሻሽ 12፡30 ላይ ገመዶ አባተ በከፍታ ዝላይ ሲወዳደር ኦታጌ ኦባንግ በወንዶች ጦር ውርወራ ይሳተፋል።
በምሽት የሚደረጉ ውድድሮች ላይ ወሰኔ አሰፋ፣ አልማዝ ዮሐንስ፣ ደራርቱ እኖታ እና ሌሎች አትሌቶች ይሳተፋሉ። ኢትዮጵያ እስካሁን 11 ሜዳሊያዎችን አስመዝግባለች።