ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ከሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ጋር ተወያይተዋል።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሩሲያ ፌዴሬሽን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ እና የልዑክ ቡድናቸው ጋር ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችና አዳዲስ የትብብር ዕድሎች ዙሪያ ውይይት አድርገናል ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) እንዲሁም ከላቭሮቭ ጋር ተወያይተዋል። ሚኒስትሮቹ በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን በብሪክስ ያለውን ትብብር ለማጠናከር ተስማምተዋል።