ኢትዮጵያ እና ጣሊያን ዛሬ የ70 ሚሊየን ዩሮ ብድር ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን እና የልማት ስራዎችን ለመደገፍ ይውላል።
የብድር ስምምነቱ በፋይናንስ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ እና በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ሴም ፋብሪዝ ተፈራርሟል።
አሕመድ ሽዴ ስምምነቱ በረጅም ጊዜ የሚከፈል ሲሆን ሀገራዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን ለማስፈጸም ይጠቅማል ብለዋል። እንዲሁም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት ያጠናክራል ብለዋል።
የጣሊያን መንግስት ለኢትዮጵያ የልማት ጥረቶች የሚሰጠውን ድጋፍ ቀጥሏል። ስምምነቱ ቀደም ሲል የተደረጉ የትብብር ማዕቀፎች አካል ነው።