የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ለሶስት አዳዲስ አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ ሰጥቷል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2018። ባለስልጣኑ ፕራይዝዎርዝ ኢንቨስትመንት ባንክ አ.ማ. በኢንቨስትመንት ባንክ ዘርፍ ፈቃድ ሰጥቷል። ብሉፊን ካፒታል አድቫይዘሪ ኃ.የተ.የግ.ማ እና ሉሚና ካፒታል ኃ.የተ.የግ.ማ ደግሞ በሰነደ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት ማማከር ዘርፍ ፈቃድ አግኝተዋል።
ባለስልጣኑ አገልግሎት ሰጪዎቹ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በዕውቀት፣ በታማኝነት እና በቁርጠኝነት እንዲወጡ አሳስቧል። በተጨማሪም ለሦስቱ አዳዲስ አገልግሎት ሰጪዎች 10 ተሿሚ እንደራሴዎች እና 15 ቦርድ አባላት ሹመት ፈቃድ መጽደቁን አመልክቷል።
በዚህ ሂደት በባለስልጣኑ ፈቃድ የተሰጣቸው የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ጠቅላላ ቁጥር 21 ደርሷል።