የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ አስመጪዎችና ላኪዎች የባንኩን የሂሳብ ቁጥር በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የአንድ መስኮት አገልግሎት በኩል እንዲያገኙ ፍቃድ ሰጥቷል።
ባንኩ ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ጋር በመተባበር አዲስ የዲጂታል አገልግሎት አስተዋውቋል። አገልግሎቱ አዲስ ፍቃድ ላወጡ አስመጪዎችና ላኪዎች የባንኩን የሂሳብ ቁጥር ያለምንም ውጣ ውረድ እንዲያገኙ ያደርጋል።
አገልግሎቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የብሔራዊ ባንክ የሂሳብ ቁጥር ለሚያወጡ ተቋማት ብቻ ይተገበራል። ቀደም ሲል የቁጥር ያላቸው ተቋማት የንግድ ግብይቶቻቸውን በነባር ቁጥራቸው መቀጠል ይችላሉ።
ይህ እርምጃ የባንኩ የንግድ አገልግሎቶችን ለማዘመንና የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥን ለማጠናከር የሚደረግ ጥረት አካል ነው።