የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ የኢትዮጵያ የካርበን ገበያ ረቂቅ አዋጅን አጽድቋል።
የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ ረቂቅ አዋጁ የካርበን ገበያ ስትራቴጂን ወደ ተግባር ለመለወጥ የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ እንደሆነ ገልጸዋል።
አዋጁ የፓሪሱን ስምምነት ጨምሮ አለም አቀፍ ውሎችን ለመተግበር እና የሙቀት አማቂ ጋዞች ልቀት ቅነሳ ቃል ኪዳኖችን ለማሟላት ይረዳል። እንዲሁም ከፍተኛ ጥራት ላለው አረንጓዴ ኢንቨስትመንትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
አዋጁ ቀደም ሲል በቂ የአሰራር ስርዓት ሳይኖር የነበረውን የግብይት ሂደት በግልጽ የህግ ማዕቀፍ እንዲመራ ያደርገዋል። በመጨረሻም የኢትዮጵያ የካርበን ገበያ አዋጅ ቁጥር 1436/2018 በአብላጫ ድምጽ ጸድቋል።