የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዴ ሃቪላንድ ካናዳ ሁለት የዲኤችሲ-6 ትዊን ኦተር ክላሲክ 300-ጂ አውሮፕላኖችን ከተወሰኑት መካከል የመጀመሪያውን በዛሬው ቀን ተረክቧል።
አዲስ አበባ ሰኔ 15 2018 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከካናዳው አውሮፕላን አምራች ኩባንያ ዴ ሃቪላንድ ካናዳ ሁለት የዲኤችሲ-6 ትዊን ኦተር ክላሲክ 300-ጂ አውሮፕላኖችን ከታቀዱት መካከል የመጀመሪያውን ተረክቧል።
አዲሶቹ አውሮፕላኖች የአየር መንገዱን የውስጥ እና የቀጣናዊ በረራ አገልግሎቶችን ለማጠናከር ይረዳሉ። በተጨማሪም ለቱሪዝም እንቅስቃሴዎች፣ ለአየር ላይ ቅኝት እና ጥናት ስራዎች፣ ለአየር አምቡላንስ አገልግሎት እና ለሌሎች ተግባራት ጠቃሚ ይሆናሉ።
አውሮፕላኖቹ የተለያዩ የገበያ ፍላጎቶችን በብቃት እና በአስተማማኝ ሁኔታ ለማሟላት እና ተደራሽነትን ለማስፋፋት ያለውን አቅም ያጠናክራሉ።