የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሞሪሺየስ ዋና ከተማ ፖርት ሉዊስ ከነገ ጀምሮ የቀጥታ በረራ ያደርጋል።
በአዲስ አበባ የተደረገው ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ቀጥታ በረራው የሁለትዮሽ ግንኙነትን ከማጠናከር ባለፈ ለሀገራቱ ዘላቂ ጥቅሞችን ይዞ እንደሚመጣ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ የሞሪሺየስ አምባሳደር ኢንድራርጂት ባቡዋ በበኩላቸው ቀጥታ በረራው በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ የሁለቱ ሀገራት ነጋዴዎች በቀላሉ እንዲገናኙ እና የጋራ ኢንቨስትመንት እንዲያቋቁሙ ምቹ እድል ይፈጥራል ብለዋል።
አየር መንገዱ ወደ ፖርት ሉዊስ በሳምንት ሶስት ቀን በረራ ያደርጋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ 145 ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች አሉት።