የከተማ አስተዳደሩ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የ2019 ዓ.ም የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ መወሰኛ ጥናት ውይይት አካሂዷል። ተመኑ ከሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል።
የቢሮው ኃላፊ ቅድስት ወ/ጊዮርጊስ እንደተናገሩት የኪራይ ቁጥጥር አዋጅ ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ሆኗል። አዋጁ ተከራዮች በአንድ ቦታ ለሁለት ዓመት እንዲቆዩ ያስችላል።
የዋጋ ጥናቱ የተከራዮችን የመክፈል አቅምና የአከራዮችን ገቢ ባገናዘበ መንገድ ተካሂዷል። ውል እድሳት በቴክኖሎጂ በታገዘ መልኩ በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ይከናወናል።