የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከኖርዌይ ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ጋር በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች አጠቃቀም ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።
በአዲስ አበባ የተካሄደው የፊርማ ሥነ ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጌቱ ገረመው እና በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ስቴይን ክሪስቴንሰን ተገኝተዋል።
ስምምነቱ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በስፋት ለማስተዋወቅ እና ዘመናዊ የኃይል አጠቃቀምን ለማሳደግ ያለመ ነው። የኖርዌይን የቴክኖሎጂ ልምድ ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት እና ለአምራች ተቋማት አቅም ግንባታ አስተዋጽኦ ለማድረግ ይረዳል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የኤሌክትሪክ መኪና መሙያ መሠረተ ልማቶችን ለመዘርጋት ለተጀመረው ስትራቴጂካዊ ጉዞ ትልቅ አጋዥ እንደሚሆን ተገልጿል።