አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሙዚቃ አዳዲስ ከዋክብት መፍለቂያ የሆነው የፋና ላምሮት ምዕራፍ 22 የድምጻውያን ውድድር የፊታችን ቅዳሜ ቀጥሎ ይካሄዳል።
ውድድሩ በተመልካቾች፣ በዳኞች እና በተወዳዳሪዎች የሙዚቃ ምርጫ እንደደመቀ ቀጥሏል። በ7ኛ ሳምንት ቅዳሜ ከምድብ አንድ አምስት ተወዳዳሪዎች ጋር ይካሄዳል። ተወዳዳሪዎቹ ሄለን ሰለሞን፣ ዳንኤል አለልኝ፣ ኤርሚያስ መንግስቴ፣ ዮናስ ሽመልስ እና የአብሥራ ገዛኸኝ ናቸው። ዛየን ባንድ በ2 ዙር ሙዚቀኞቹን ያጅባል።
በተመልካች እና በዳኞች ድምር ውጤት ዝቅተኛ ነጥብ ያመጣ አንድ ተወዳዳሪ ይሰናበታል። ለፍጻሜ ለሚደርሱ አራት ተወዳዳሪዎች የ1 ሚሊየን ብር ሽልማት የተዘጋጀላቸው ሲሆን ለፋና ላምሮት 6ኛው የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር በቀጥታ ያልፋሉ።
ውድድሩን ቅዳሜ ከቀኑ 6:00 ጀምሮ በፋና ቴሌቪዥን፣ በፋና+፣ በፋና ፌስቡክ፣ በፋና ዩቲዩብ እና ቴሌግራም ገጾች እንዲሁም በ www.fanamc.com በቀጥታ ይከታተሉ።