የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ በለንደን የአየር ንብረት የድርጊት ሳምንት ላይ ሀገራት ተባብረው አዳዲስ መፍትሄዎችን እንዲተገብሩ ጠይቀዋል።
ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ሰኔ 15 ቀን 2018 በለንደን ስቶክ ኤክስቼንጅ የዕለቱን ግብይት በይፋ ከፍተዋል። እየጨመረ የመጣው የአየር ንብረት ለውጥ ተቀናጅቶ ዓለም አቀፍ ምላሽ እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።
ዩናይትድ ኪንግደም ከፍተኛ ሙቀት እያጋጠማት መሆኑን ጠቅሰው ማንኛውም ሀገር ብቻውን ቀውሱን መፍታት እንደማይችል አጽንኦት ሰጥተዋል። በመድረኩ ላይ የተገኙ ባለድርሻ አካላት ተግባራዊ መፍትሄዎችን በጋራ ለማዘጋጀት ጥሪ አቅርበዋል።
ሚኒስትሩ ሀብት፣ የጋራ እውቀት እና ቁርጠኝነት በማጣመር ለመላው ዓለም የሚጠቅሙ ስትራቴጂዎችን ማዘጋጀት እንዳለብን ተናግረዋል።