የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ ከዓለም ባንክ የኦፕሬሽን ማኔጂንግ ዳይሬክተር አና ቤርዴ ጋር ተወያይተዋል። ስብሰባው በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
ሚኒስትሩ ቀጣይነት ያለው የኢትዮጵያ ሪፎርም እንቅስቃሴና የመንግሥት ትኩረት አቅጣጫ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በተጨማሪም በመጪው የዓለም ባንክና የኢትዮጵያ ስትራቴጂያዊ አጋርነት ማዕቀፍ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮችን አካፍለዋል።
አና ቤርዴ የኢትዮጵያ መንግሥት የወሰደውን ጠንካራ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራና አዎንታዊ የኢኮኖሚ ለውጦች አድንቀዋል። ባንኩ ኢትዮጵያ የሪፎርም አጀንዳዎችንና የረጅም ጊዜ የልማት ግቦችን ለማሳካት በምታደርገው ጥረት ድጋፉን እንደሚያጠናክር አረጋግጠዋል።