አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) - በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ በዘመን አይሽሬ እና ባሕላዊ ስራዎቿ የብዙዎችን ልብ የማረከችው አንጋፋዋ ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ በአዲስ አበባ ይፈጸማል።
ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች። በኪነ ጥበብ ህይወቷ በርካታ የማይረሱ ድንቅ ስራዎችን ለህዝብ አበርክታለች።
እሷ የሁለት ወንድና የአራት ሴት ልጆች እናት ነበረች። የቀብር ሥርዓቱ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ደብረ ምህረት ሰዓሊተ ምህረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴደራል ቀን 8 ሰዓት ላይ ይፈጸማል።