የማክሮኢኮኖሚ ማሻሻያ የዋጋ ንረትን በመቆጣጠር ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል አሉ አቶ አህመድ ሺዴ

የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ የማክሮኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ የዋጋ ንረትን በመቆጣጠር ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳደረገ ተናግረዋል።

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የገንዘብ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት የ2018 የበጀት ዓመት አፈጻጸም እንዲሁም የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይት አካሂደዋል።

አቶ አህመድ ሺዴ በመድረኩ እንዳሉት የማክሮኢኮኖሚ ማሻሻያው አፈጻጸም እጅግ ውቤታማ ነው። ይህ ጠንካራ አፈጻጸም በተለይም የዋጋ ንረትን በመቆጣጠር፣ የሀገር ውስጥ ገቢን በማሳደግና ከልማት አጋሮች ጋር የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ነው ያነሱት።

በተጨማሪም በ2018 በጀት ዓመት ከዓለም አቀፍ አበዳሪ አካላት ጋር በተደረገው የብድር ዕዳ ሽግሽግ ስምምነት መሰረት የዕዳ መክፈል የተጀመረበት ውጤታማ ዓመት እንደነበር ጠቁመዋል። የማክሮኢኮኖሚ ማሻሻያው ትግበራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፣ በሕዝበ ተወካዮች ምክር ቤት የጸደቀውን በጀት ውጤታማ በሆነ መንገድ ስራ ላይ ለማዋል በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።

ተያያዥ ጽሁፎች

Finance Minister Ahmed Shide said international financial institutions must improve their practices to help countries prevent crises. He made the remarks at an ongoing global partnership forum in London.

በAI የተዘገበ

Finance Minister Ahmed Shide reported to parliament that the 1.93 trillion birr federal budget is under pressure from delayed external aid. He addressed lawmakers on May 4, 2026, noting that domestic borrowing has risen faster than planned. The session took place without private media present.

The International Monetary Fund has called on Ethiopia's central bank to stand ready to tighten monetary policy if inflation pressures return, following approval of the fifth review under a credit facility that released about $464 million.

በAI የተዘገበ

The Finance Ministry presented its transition report with macroeconomic data from the outgoing administration.

ይህ ድረ-ገጽ ኩኪዎችን ይጠቀማል

የእኛን ጣቢያ ለማሻሻል ለትንታኔ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። የእኛን የሚስጥር ፖሊሲ አንብቡ የሚስጥር ፖሊሲ ለተጨማሪ መረጃ።
ውድቅ አድርግ