የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ የማክሮኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ የዋጋ ንረትን በመቆጣጠር ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳደረገ ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የገንዘብ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት የ2018 የበጀት ዓመት አፈጻጸም እንዲሁም የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይት አካሂደዋል።
አቶ አህመድ ሺዴ በመድረኩ እንዳሉት የማክሮኢኮኖሚ ማሻሻያው አፈጻጸም እጅግ ውቤታማ ነው። ይህ ጠንካራ አፈጻጸም በተለይም የዋጋ ንረትን በመቆጣጠር፣ የሀገር ውስጥ ገቢን በማሳደግና ከልማት አጋሮች ጋር የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ነው ያነሱት።
በተጨማሪም በ2018 በጀት ዓመት ከዓለም አቀፍ አበዳሪ አካላት ጋር በተደረገው የብድር ዕዳ ሽግሽግ ስምምነት መሰረት የዕዳ መክፈል የተጀመረበት ውጤታማ ዓመት እንደነበር ጠቁመዋል። የማክሮኢኮኖሚ ማሻሻያው ትግበራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፣ በሕዝበ ተወካዮች ምክር ቤት የጸደቀውን በጀት ውጤታማ በሆነ መንገድ ስራ ላይ ለማዋል በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።