የአፍሪካ ኅብረት በቀይ ባሕር ቀጣና ለዘላቂ ሰላም የሚደረጉ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶችን ሙሉ በሙሉ እንደሚደግፍ አስታውቋል።
የኅብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ማሀሙድ አሊ ዩሱፍ ባወጡት መግለጫ በቀይ ባሕር የውኃ መስመር ላይ በንግድ መርከቦች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች ለቀጣናው ከፍተኛ ስጋት መሆናቸውን አመልክተዋል።
ሊቀመንበሩ ሁቲዎች በሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት ላይ የባሕር ላይ እገዳ ካወጁ በኋላ በነዳጅ ጫኝ መርከቦች ላይ የተፈጸሙ ጥቃቶችን አጥብቀው አውግዘዋል።
እነዚህ ጥቃቶች ዓለም አቀፍ አቅርቦት ሰንሰለትን፣ የነዳጅ ዋስትናን እና የአፍሪካ ሀገራትን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም አደጋ ላይ ይጥላሉ ተብሏል። ሊቀመንበሩ ተመሳሳይ ጥቃቶች እንዲቆሙ እና ዓለም አቀፍ ሕጎች እንዲከበሩ ጥሪ አቅርበዋል።