ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የመደመር የሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ ግንባታ በጥቂት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትምህርት ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን ገልጸው የታችኛው የትምህርት መሠረት ላይ ትኩረት እንደተደረገ አመልክተዋል። ባለፉት ሰባት ዓመታት አዳዲስ መደበኛ ዩኒቨርሲቲዎች እንዳልተገነቡ ገልጸዋል።
ይሁን እንጂ የሰው ሠራሽ አስተውሎትና ቴክኖሎጂ ሽግግርን በመገንዘብ ዘመናዊ የሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ ግንባታ በጥራት እየተከናወነ መሆኑን አመልክተዋል። ዩኒቨርሲቲው በመላው አፍሪካ ተወዳዳሪ እንደሌለው ተናግረዋል።
ይህ ግንባታ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የተደረገው አካል እንደሆነ ተገልጿል።