የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ባህላዊ የቤት አሰራር የከተሞችን የቤት እጥረት መፍታት እንደማይችል ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ግንባታ ቦታን ጎብኝተዋል።
ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ በአዲስ አበባ በዛሬው እለት የተደረገውን ጉብኝት ተከትሎ የከተሞችን እድገት በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በተለይም በ67 ከተሞች የሚተገበረው የኮሪደር ልማት ከተሞችን ጽዱና ምቹ አድርጓል ብለዋል።
ባለፉት አምስት ዓመታት 1.2 ሚሊየን ቤቶች መገንባታቸውን አመልክተዋል። ይህ ቁጥር ካለፉት 16 እና 17 ዓመታት 160 ሺህ ቤቶች ጋር ሲነጻጸር ትልቅ መሻሻል እንደሆነ ገልጸዋል።
ሚኒስቴሩ ለመጀመሪያ ጊዜ የቤቶች ፖሊሲን በማጽደቅ ላይ መሆኑን አብራርተዋል። የ3ዲ ኮንክሪት ህትመትና የቅድመ ዝግጅት ብረት ግንባታ ዘዴዎችን በመጠቀም የቤት ተደራሽነትን ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።