በአዲስ አበባ አምባሳደር ለምለም ፍስሃ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ለአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የሹመት ደብዳቤያቸውን አቀረቡ።
በዚህ ወቅት ሁለቱ ወገኖች በአህጉራዊ፣ ዓለም አቀፋዊ እና በሕብረቱ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።
የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር እንዳሉት አምባሳደር ለምለም ያላቸው ልምድ እና የአመራር እውቀት በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ሕብረት መካከል ያለውን ትብብር የበለጠ ያጠናክረዋል።
ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ሕብረት የምታደርገውን ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አድንቀው ኢትየጵያ ያካሄደችው ምርጫ ሰላማዊና ስርዓት ባለው መልኩ የተከናወነ መሆኑን አንስተዋል።
አምባሳደር ለምለም ፍስሃ በበኩላቸው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረትን እና አህጉራዊ አጀንዳዎችን ለመደገፍ ያላትን ጠንካራ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።