የብሩንዲ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ኤድዋርድ ቢዚማና በአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።
አምባሳደር ቢዚማና ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፕሮቶኮል ሹም መላኩ በዳዳ ተቀብለዋቸዋል።
እነርሱ በ49ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚዎች ም/ቤት ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል።
ጉባኤው ሐምሌ 21 እና 22 በአዲስ አበባ ይካሄዳል። መሪ ሀሳቡም “የአጀንዳ 2063 ግቦችን ለማሳካት ዘላቂ የውሀ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንፅህና አጠባበቅ ስረዓቶችን ማረጋገጥ” ነው።