የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ኢትዮጵያ በመግዛት አቅም ተመጣጣኝነት በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ መሆኗን አመለከተ።
በአዲስ አበባ የተገለጸው ሪፖርት ኢትዮጵያ በዓመታዊ የመግዛት አቅም ተመጣጣኝነት የሚለካ 558 ነጥብ 93 ቢሊየን ዶላር ዓመታዊ ጥቅል ምርት እንዳላት ያሳያል።
ይህ አኃዝ ኬንያን እና ታንዛኒያን ያስቀድማል። የሦስቱ ሀገራት ድምር ደግሞ 1 ነጥብ 35 ትሪሊየን ዶላር ይደርሳል።
ይህ አቅም ከአራተኛ እስከ 19ኛ ደረጃ ላይ ካሉ ሀገራት በጠቅላላ እንደሚበልጥ ሪፖርቱ ገልጿል።