የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ከ25.4 ቢሊየን ብር በላይ በጀት አጽድቋል። ይህ በጀት ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር 30 በመቶ ዕድገት አሳይቷል።
የክልሉ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን አጠናቅቋል። የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ዚያድ አብዱላሂ በጀቱ ከክልሉ ገቢ፣ ከፌዴራል ድጎማ እና ሌሎች ምንጮች የሚገኝ መሆኑን አመልክተዋል።
ከበጀቱ ውስጥ 15.1 ቢሊየን ብር በክልሉ ከሚሰበሰብ ገቢ ይሸፈናል። የታቀደው ገቢ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር 40 በመቶ ጭማሪ አለው።
በጀቱ ለመደበኛ እና ለልማት ሥራዎች ይውላል። የክልሉ ወጪ በራሱ ገቢ ለመሸፈን ጥረት እየተደረገ ነው።