ከንቲባ አዳነች የበጎ ፈቃድና የልማት ሥራዎችን በጥብቅ ቅንጅት እንዲመሩ ጠየቁ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የበጎ ፈቃድና የልማት ሥራዎችን በጥብቅ ቅንጅት መምራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ከንቲባዋ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ የአረንጓዴ ዐሻራ፣ የቤት ግንባታና የማህበራዊ ድጋፍ ሥራዎችን አፈጻጸም ከከተማዋ አመራሮች ጋር ገምግመዋል። በክፍለ ከተሞችና በተቋማት መካከል የአፈጻጸም ልዩነቶች በመኖራቸው ቀጣይ ሥራዎች በጥብቅ ቅንጅት ሊመሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የቤት ግንባታን ማፋጠን፣ የፍሳሽ ማለፊያ ዲችዎችን ማጽዳትና አዳዲስ ግንባታዎችን ማካሄድ እንዲሁም ከፍተኛ ሃብት ወጥቶባቸው የለመሩ ሥፍራዎችን አሰራርና ጽዳት በአግባቡ መጠበቅ ላይ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ አመልክተዋል። በግንባታ ምክንያት በሚወጡ ተረፈ ምርቶች መንገዶችን የሚያበላሹ እና ዲችዎችን የሚዘጉ አካላት ችግሩን በአፋጣኝ እንዲያርሙና ተጠያቂ እንዲሆኑ የማድረግ ሥራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

የችግኝ ተከላ ከዕቅድ በላይ እንዲከናወንና ለአስፈላጊው ጥራት ትኩረት እንዲሰጥ እንዲሁም የበጎ ፈቃድ አገልግሎትንና የከተማ ጽዳትን የሕብረተሰቡ ባሕል የማድረግ ሥራ በትኩረት እንደሚከናወን ጠቁመዋል። የተማሪዎችን ውጤታማነት ለማረጋገጥ የሚሰጠው የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርትና የጎልማሶች ትምህርት በልዩ ትኩረት እንደሚመሩም አስፍረዋል።

ተያያዥ ጽሁፎች

Addis Ababa Mayor Adanech Abiebe has called on the city's youth to actively take part in social and voluntary activities.

በAI የተዘገበ

Addis Ababa Mayor Adanech Abebe has launched the 2018 E.C. summer cleaning campaign.

The Addis Ababa city administration has begun reviewing its performance for the 2018 budget year. Mayor Adanech Abiebe announced that goals set during the year will be assessed over three days.

በAI የተዘገበ

Addis Ababa Mayor Adanech Abiebe has handed over a five-story building with 44 homes and shops to beneficiaries in the Gabs Tera area.

 

 

 

ይህ ድረ-ገጽ ኩኪዎችን ይጠቀማል

የእኛን ጣቢያ ለማሻሻል ለትንታኔ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። የእኛን የሚስጥር ፖሊሲ አንብቡ የሚስጥር ፖሊሲ ለተጨማሪ መረጃ።
ውድቅ አድርግ