የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት ከ55 ሚሊየን በላይ ዜጎች የህክምና አገልግሎት እንዳገኙ አስታወቀ።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ተስፋዬ ወርቁ እንደተናገሩት አገልግሎቱ በ1ሺህ 279 ወረዳዎች ተደራሽ ሆኗል። በበጀት ዓመቱ ከ10 ነጥብ 7 ሚሊየን በላይ ዜጎች አባል ሆነዋል።
ከ10 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ ለህክምና ተቋማት ተከፍሏል። ከዚህ በተጨማሪ 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች ነፃ አገልግሎት አግኝተዋል።
የአገልግሎቱ የስራ አፈፃፀም ግምገማ በጎንደር ከተማ እየተካሄደ ነው።