የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ ሰዓዳ አብዱረህማን የገዳ ሥርዓት የሕዝብን የራስን የማስተዳደር መብት እንደሚያረጋግጥ ተናግረዋል።
አዲስ አበባ ላይ በተካሄደው የ71ኛው የቱለማ ገዳ ሥርዓት የአለንጌ ርክክብ ፓናል ውይይት ላይ ወሮ ሰዓዳ ይህን አስተያየት ሰጥተዋል።
የገዳ ሥርዓት የኦሮሞ ሕዝብ ለሀገርና ለዓለም ያበረከተው እና ስልጣን በሰላማዊ መንገድ የሚሸጋገርበት ሥርዓት እንደሆነ አስረድተዋል።
የቱለማ ገዳ ስልጣን ሽግግር ሥነ ሥርዓት ከሰኔ 4 እስከ 7 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይካሄዳል።