የግብርና ሚኒስቴር ክልሎችና ከተማ አስተዳድሮች ለዘንድሮው የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ከ800 ሚሊየን በላይ ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት አጠናቅቀዋል ብሏል።
የሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ይመር ዳውድ ለፋና ዲጂታል እንደተናገሩት በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ 8 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል በቁርጠኝነት እየተሰራ ነው።
የፊታችን ሰኞ በሚከናወነው መርሐ ግብር ከ800 ሚሊየን በላይ ችግኞች በ291 ሺህ 617 ሔክታር መሬት ላይ በ10 ሺህ 941 ቦታዎች ይተከላሉ። ኦሮሚያ ክልል 476 ነጥብ 6 ሚሊየን ችግኞች፣ አማራ 308 ነጥብ 7 ሚሊየን ችግኞች እና ሌሎች ክልሎች ተመዝግበዋል።
የችግኝ መትከያ ጉድጓዶች መቆፈር፣ ጂኦሪፈረንስ እና ችግኞችን ማድረስ ሥራዎች ተጠናቀቀዋል። ይመር ዳውድ መላው ኢትዮጵያውያን በመርሐ ግብሩ እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።