የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ሦስተኛው ዙር የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ በአፋር ክልል መጀመሩን አስታውቋል። ይህ ንቅናቄ ለሦስት ወራት ይቆያል።
በአዲስ አበባ የተደረገው መግለጫ እንደሚያመለክተው ዋና ዳይሬክተር ለሊሴ ነሚ (ዶ/ር) ባለፉት ሁለት ዓመታት ሰፊ ማህበረሰብ መድረስ መቻሉን ተናግረዋል።
በዚህ ዙር በፕላስቲኮች፣ ኬሚካሎችና የድምፅ ብክለት ላይ ትኩረት ይደረጋል። ልማቶች አካባቢን ሳይበክሉ መተግበር እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።
በተጨማሪም ባለስልጣኑ ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢኒስቲትዩት ጋር የአካባቢ ብክለት ዲጂታል ሪፖርት ማድረጊያ መተግበሪያ አስተዋውቋል። ተጠቃሚዎች በቪዲዮ፣ ፎቶ እና ፅሁፍ ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።